CATHOLIC EPARCHY OF EMDIBIR
  • About us
  • Home
  • Eparchy
    • Vision & Mission
    • Parishes
    • Leadership
  • Pastoral
    • Pastoral Coordinating office
    • Projects >
      • Bible Study and Catechist
      • Education
      • Family & laity Apostolate
      • Justice & Peace
      • Small Christian Community
      • YCW & Youth Apostolate
  • Bible Correspondence
  • Social & Development
    • Social & Development Commission Coordination Office
    • Projects >
      • Health
      • WASH
      • Livelihood & Food Security
      • Social and women's affairs >
        • BGTE
  • Resources
    • Articles
    • Events
    • Annual Reports
    • Links
  • OUR SUPPORTORS
  • CONTACT US
  • VOLUNTEER

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት በአማርኛ ቋንቋ 
(Bible study in Amharic)

ትምህርት አንድ

መጽሐፍ ቅዱስ ማለት ምን ማለት ነው/ የቃሉ አመጣጥ ከወዴትና ምንስ ያመለክታል? 
​መጽሐፍ ቅዱስ ቃሉ እንደሚያመለክተው መጽሐፍ እና ቅዱስ የሚሉ የሁለት ቃላት ጥምረት ነው፡፡ በግሪክ ቋንቋ ቢብሎስ (byblos) ከደንገል በተሠራ ወረቀት ወይም በብራና ከተጻፈ በኋላ በሁለት በትሮች የሚጠቀለል መጽሐፍ ያመለክታል፡፡ ቢብሎስ በእንግሊዝኛው ባይብል ተብሎ ሲተረጎም በአማርኛው ደግሞ መጽሐፍ በሚለው ቃል ተተረጎመ፡፡ የግሪኩ ቃል ቢብሎስ (byblos) እራሱ ቢብሎሰ (byblos) ከተባለ ከተማ ስም የተገኘ ነው፤ እርሱም ከኒቂያ ወደቦች መካከል በቤይሩት 25 ማይል ያህል የሚገኝ አገር ነው፡፡ለመጽሐፍ ያገለግል ዘንድ ፓፒረስ (ደንገል) የተባለውን ተክል እንደ ወረቀት አድርገው ይሠሩበት የነበረ ቦታ ነው፡፡                                                                   
ቀጣዪን ከዚህ ያንብቡ...

Recent Posts

All

Topics​

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ማለት ነው
የቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር 
የቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር ታሪክ
እግዚአብሔር አብርሃምን ለምን ለይቶ ጠራው? 
ዘጸአት ማለት ምን ማለት ነው?
ዐሥራት ማለት ምን ማለት ነው? ​
​

Archives

March 2021
October 2018
July 2018
June 2018
May 2018
April 2018

bible_study__lesson-one-1_.pdf
File Size: 216 kb
File Type: pdf
Download File

RSS Feed

March 05th, 2021

3/6/2021

0 Comments

 
0 Comments

የኦሪት ዘጸአት ጥናት

10/21/2018

0 Comments

 
ከሙሴ ዘመን በፊት ከአብርሃም ጊዜ ጀምሮ ዐሥራት መክፈል የተለመደ ነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፤ ለመሆኑ ዐሥራት ማለት ምን ማለት ነው? አጀማመሩስ እንዴት ነው?
ዐሥራት ማለት አንድ ዐሥረኛ ማለት ነው፡፡ ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ ከማንኛውም ገቢ ዐሥረኛው እጅ ለሃይማኖት መሪዎች ወይም ለመንግሥት ይሰጥ ነበር፡፡ ነገር ግን እንዴት እንደተጀመረ አይታወቅም፡፡ ከሙሴ ዘመን በፊትና እንዲሁም ከባቢሎን እስከ ሮም ድረስ ይሠራበት ነበር፡፡ አብርሃም ለመልከ ጼዴቅ ዐሥራትን ሰጠው (ዘፍ. 14፡20)፡፡ ያዕቆብም ለእግዚአብሔር ዐሥራትን ለመክፈል ተሳለ(ዘፍ. 28፡22)፡፡ ሌዋውያን ካህናት እንዲጠቀሙበት(ዘኁ 18፡21-32)፣ ምድር ከምታፈራውና ከከብትም ወገን ዐሥራት እንዲሰጥ ታዘዘ (ዘሌ 27፡30-33)፡፡ የሚከፈልበት ጊዜ ተወሰነ (ዘዳ. 12፡5-18፤ 14፡22-29)፡፡ ዐሥራትም ሲከፍሉ እግዚአብሔር ሕዝቡን ይባርካል(ዘዳ 26፡13-15፤ ሚል 3፡10)፡፡ ፈሪሳውያን ከቅመማ ቅመም ሳይቀር ዐሥራት ይከፍሉ ነበር(ማቴ 23፡23)፡፡ ሐዋርያት ስለ ዐሥራት አልጻፉም፤ ሆኖም  
ቀጣዪን ከዚህ ያንብቡ
bible_study-lesson-six__6_.pdf
File Size: 225 kb
File Type: pdf
Download File

0 Comments

ዘጸአት ማለት ምን ማለት ነው?

7/23/2018

0 Comments

 
ዘጸአት  ሁለተኛው የሙሴ መጽሐፍ ሲሆን “ጸአት” ማለት መውጣት ማለት ነው፡፡መውጣት ሲባል አንድን ቦታ ለቆ መውጣት ወይም ከባርነት ነፃ መውጣት ሊሆን ይችላል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ለእግዚአብሔር የተለዩት እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነፃ እንደወጡና ወደ ከነዓን ምድር እንደተጓዙ እናነባለን፡፡ በአጠቃላይ እስራኤላውያን ከግብጽ የባርነት ኑሮ ነፃ መውጣታቸውንና ወደ ተስፋዪቱ ምድር ጉዞ መጀመራቸውን የሚተርክ መጽሐፍ ስለሆነ “ዘጸአት” ተባለ፡፡   ቀጣዪን ከዚህ ያንብቡ...
bible_study_lesson-5.pdf
File Size: 257 kb
File Type: pdf
Download File

0 Comments

እግዚአብሔር አብርሃምን ለምን ለይቶ ጠራው?

6/6/2018

0 Comments

 

ትምህርት አራት

►እግዚአብሔር አብርሃምን ለምን ለይቶ ጠራው?
ይህንን ጥያቄ ከመመለሳችን በፊት ጥሪ ወይም መጠራት ማለት ምን ማለት ነው የሚለውን እናስቀድም፡፡ እግዚአብሔር ሁሉንም ሰው ወደ ልጁ የሠርግ ግብዣ ይጠራል(ማቴ 22፡ 3-9)፤ ይህም ማለት እግዚአብሔር ኃጢአተኞችን በወንጌል በኩል ለደኅንነት ይጠራል(ኢሳ 55፡ 1፣ ዮሐ 3, 16፣ ሐዋ 12፡ 30)፡፡ የወንጌሉን ጥሪ ግን ሁሉም አይቀበሉም፤ የሚቀበሉት በልቡናቸው ልዩ የእግዚአብሔር ጥሪ ሲሰማቸው ብቻ ነው(ማቴ 13፡ 9፣ 22, 14፣ ዮሐ 6፡ 44)፡፡ የዚህ ዓይነቱ ጥሪ የንስሓ ጥሪ በመባል ይታወቃል(ሉቃ 5፡ 32፣ ማር 2፡ 17 ማቴ 9፡ 13)፡፡ ይህ ጥሪ ለነፃነትና ከክርስቶስ ጋር ኅብረት እንዲኖረን ነው(1 ቆሮ 1፡ 9፣ ገላ 5፡ 13)፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ እግዚአብሔር አንድን ግለ ሰው ብቻ ለይቶ ለተለየ አገልግሎት ይጠራል፡፡ ለምሳሌ አብርሃም፣ ሙሴ እና ነቢያቶች መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይህ የተጠራው ሰው ሙሉ የሆነ ነፃነት ስላለው ጥሪውን የመቀበል ወይም ያለመቀበል መብት አለው፡፡ ጥሪውን ከተቀበለ እግዚአብሔር ለዚህ ሰው አንድ ልዩ የሆነ ተልእኮ ይሰጠዋል፡፡ ቀጣዪን ከዚህ ያንብቡ...
bible_study__lesson-4_.pdf
File Size: 266 kb
File Type: pdf
Download File

0 Comments

ትምህርት ሦስት

5/18/2018

 

በቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር ውስጥ ከታሪክና ከዓመታትም አኳያ የመጀመሪያዎች ናቸው ተብለው የሚታወቁት የትኞቹ ናቸው?

የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያውን ክፍል ይዘው የሚገኙት የሕግ መጻሕፍት ወይም የሙሴ መጻሕፍት ወይም ደግሞ የኦሪት መጻሕፍት(ብሔረ ኦሪት) በመባል የሚታወቁትን ነው፡፡ እነዚህም፦ዘፍጥረት፣ዘጸአት፣ዘሌዋውያን፣ዘኊልቅናዘዳግምናቸው፡፡
► ዘፍጥረት ማለት ምን ማለት ነው?
    ዘፍጥረት የተባለበት ምክንያት ስለፍጥረትና የፍጥረት ሁሉ ፍጻሜ ስለሆነው ስለ ሰው ፍጥረት ስለሚናገር ነው፡፡ ዘፍጥረት ስለ ዓለም አፈጣጠር፣ ስለ ሰው አፈጣጠር፣ እግዚአብሔር ከሰው ጋር ስለ መሠረተው ቃልኪዳንና ሰው በኃጢአት ስለመውደቁ እንዲሁም ስለ ቀደሙት አባቶች አኗኗር ይተርካል፡፡ እግዚአብሔር ሰውን በመልኩ 
እንደ ምሳሌው ሲፈጥር ሙሉ ነፃነት ይኖረው ዘንድ እንደወደደ በነፃነቱም ይጠቀም ዘንድ ትእዛዝ እንደሰጠው መጽሐፉ ይናገረናል(ዘፍ 1-2)፡፡ ቀጣዪን ከዚህ ያንብቡ...
​
bible_study_lesson-3_.pdf
File Size: 277 kb
File Type: pdf
Download File

ትምህርት ሁለት (የመጽሐፍ ቅዱስ መግቢያ)

4/4/2018

0 Comments

 
​ የቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር እንዴት ይገለጻል? ቅዱሳት መጻሕፍት የትኞቹ ናቸው?
በትምህርት አንድ ላይ ለማብራራት እንደተሞከረው የቅዱሳት መጻሕፍት ዝርዝር በግሪክና በእንግሊዝኛ “ካኖን” ተብሎ ይጠራል፡፡ “በካኖን” ውስጥ የተዘረዘሩት የብሉይና የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት በሙሉ (ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ዮሐንስ ራእይ) እግዚአብሔር ያስጻፋቸው ወይም ሰዎች በእግዚአብሔር መንፈስ ተሞልተውና ተመርተው የጻፏቸው ናቸው፤ ዋና የክርስቲያን መመሪያ ናቸው (ሮሜ. 15፡4፤ 2ጢሞ. 3፡16-17)፡፡ በዚህም ምክንያት ቅዱሳት መጻሕፍት በመባል ይታወቃሉ፡፡ እነዚህ መጻሕፍት ዝርዝራቸውና ተቀባይነታቸው በሁሉም ሃይማኖቶች ዘንድ አንድ አይደለም (አንድ ዓይነት ወይም ወጥ የሆነ ተቀባይነት የላቸውም)፡፡
 ቀጣዩን ከዚህ ያንብቡ...
bible_study__lesson-two_.pdf
File Size: 196 kb
File Type: pdf
Download File

0 Comments

    ​

WHO WE ARE 

Mission 
Vision
Parishes
Contact

PASTORAL

Bible Study
Education
Small Christian Community 
Family & Laity 
YCW & Youth 
Catechist

SOCIAL  & DEVELOPMENT

Health
Wash
Livelihood & Food Security
Social Rehabilitation

ResOURCEs 

Article
Events
Useful Links
Reports

Copyright ©2021  Ethiopian Catholic Eparchy of Emdibir.
  • About us
  • Home
  • Eparchy
    • Vision & Mission
    • Parishes
    • Leadership
  • Pastoral
    • Pastoral Coordinating office
    • Projects >
      • Bible Study and Catechist
      • Education
      • Family & laity Apostolate
      • Justice & Peace
      • Small Christian Community
      • YCW & Youth Apostolate
  • Bible Correspondence
  • Social & Development
    • Social & Development Commission Coordination Office
    • Projects >
      • Health
      • WASH
      • Livelihood & Food Security
      • Social and women's affairs >
        • BGTE
  • Resources
    • Articles
    • Events
    • Annual Reports
    • Links
  • OUR SUPPORTORS
  • CONTACT US
  • VOLUNTEER